#Amahra
በአማራ ክልል አዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ጓጉሳ እሽኩዳዶ ወረዳ፣ “ የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ንጹሐንን ገድለዋል ” ሲሉ ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪዎች ፤ በአካባቢው ከ16 በላይ ንጹሐን መገደላቸው እና ከ37 በላይ ወጣቶች ታፍነው መወሰዳቸውን አመልክተው " ይንን ያደረጉት የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ናቸው " ብለዋል።
ግድያው የተፈጸመው አሽፋ ማርያም፣ አሽፋ አዲስ ዓለም እና ወንጀላ በሚባሉት ቦታዎች ከሰኔ 2 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ እንደሆነ ጠቁመዋል።
አሽፋ ቀበሌ 8 ሰዎች መገደላቸውን ከ8ቱ 2ቱ ቄሶች እንደሆኑ አንዲት እመጫትም ከእነ ልጇ እንደተገደለች ቀሪዎቹ ደግሞ ከ15 ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች እንደሆኑ አስረድተዋል።
ነዋሪዎቹ ፥ በወረዳው ' ፋኖዎች ' እንደነበሩ ከዛ በፊት መከላከያ እንዳልገባ ፤ ያለፈው እሁድ ግን ሌሊት 9 ሰዓት አካባቢ ከገባ በኋላ እዛ የነበሩ ፋኖዎች ምንም ሳይታኮሱ ነው ቦታውን ለቀው እንደሄዱና ከዛ በኋላ ንጹሐን እንደተገደሉ ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም የነዋሪዎቹን ቃል ይዞ የዞኑን የጸጥታ ኃላፊ አቶ ጌታቸው ቢሻውን አነጋግሯል።
" ነዋሪዎች ከ16 በላይ ንጹሐን ተገድለዋል፣ ከ37 በላይ ወጣቶች ታፍነው ተወስደዋል " ብለዋል ይህ ለምን ተደረገ ? በማለት ጠይቀናቸዋል።
አቶ ጌታቸው ፤ " እኔ የጸጥታ ኃላፊ ሆኘ የምመራው አካባቢ ላይ የደረሰ ማንኛውም አይነት ጥቃት የለም። ኦፕሬሽን የተሰራበት አሽፋ ቀበሌ ነው። በስነ ስርዓት የጽንፈኛ ካምፕ ነው የወደመው " ብለዋል።
" ሐሙስ በነበረው ኦፕሬሽን ላይ በተመሳሳይ ከዛ የተረፈው የታጠቀ ኃይል እንጂ መንግስት የቆመው ለንጹሐን ህዝብ ነው " ሲሉ አክለዋል።
ታዲያ ሳይገደሉባቸው ማልቀስን ከየት አመጡት ? በማለት ለቀረበላቸው ጥያቄ " ንጹሐን ሰዎች አልተጎዱም " ብለው ፤ " የጸጥታ ኃይል ላይ ብረት ያነሳ፣ የተኮሰ ኃይል ሰላማዊ ኃይል ነው ብለን አናምንም " ሲሉ መልሰዋል።
እንደ ጸጥታ ዘርፍ ኃላፊነትዎ የሞቱ ንጹሐን እንዳሉ ያውቃሉ ? ወጣቶቹስ የት ገቡ ? ለሚለው ጥያቄ ፥ " የሞቱ ሰዎች ፅንፈኞች ናቸው በእኛ እውቅና። ነገም እንዲህ አይነት እርምጃ እንወስዳለን " ብለዋል።
አክለው፣ " ሐሙስ በነበረ ኦፕሬሽን ላይ 3 ሰዎች በውጊያ መካከል ተይዘዋል። ሰላማዊ ሰዎች ናቸው፤ አሉ በሕይወት። ሕጋዊ የማጣራት ሥራ ይሰራባቸዋል። 37 ሰዎች አይደሉም " ነው ያሉት።
" ከዚያ ውጪ አሽፋ ላይ ደግሞ የተያዘ ሰው የለም። በውጊያ መካከል እርምጃ የተወሰደበት ሰው ሊኖር ይችላል " ያሉት ኃላፊው፣ " ውጊያ መካከል ንጹሐን ላይ ጉዳት አይደርስም ማለት አይደለም " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
በአማራ ክልል አዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ጓጉሳ እሽኩዳዶ ወረዳ፣ “ የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ንጹሐንን ገድለዋል ” ሲሉ ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪዎች ፤ በአካባቢው ከ16 በላይ ንጹሐን መገደላቸው እና ከ37 በላይ ወጣቶች ታፍነው መወሰዳቸውን አመልክተው " ይንን ያደረጉት የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ናቸው " ብለዋል።
ግድያው የተፈጸመው አሽፋ ማርያም፣ አሽፋ አዲስ ዓለም እና ወንጀላ በሚባሉት ቦታዎች ከሰኔ 2 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ እንደሆነ ጠቁመዋል።
አሽፋ ቀበሌ 8 ሰዎች መገደላቸውን ከ8ቱ 2ቱ ቄሶች እንደሆኑ አንዲት እመጫትም ከእነ ልጇ እንደተገደለች ቀሪዎቹ ደግሞ ከ15 ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች እንደሆኑ አስረድተዋል።
ነዋሪዎቹ ፥ በወረዳው ' ፋኖዎች ' እንደነበሩ ከዛ በፊት መከላከያ እንዳልገባ ፤ ያለፈው እሁድ ግን ሌሊት 9 ሰዓት አካባቢ ከገባ በኋላ እዛ የነበሩ ፋኖዎች ምንም ሳይታኮሱ ነው ቦታውን ለቀው እንደሄዱና ከዛ በኋላ ንጹሐን እንደተገደሉ ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም የነዋሪዎቹን ቃል ይዞ የዞኑን የጸጥታ ኃላፊ አቶ ጌታቸው ቢሻውን አነጋግሯል።
" ነዋሪዎች ከ16 በላይ ንጹሐን ተገድለዋል፣ ከ37 በላይ ወጣቶች ታፍነው ተወስደዋል " ብለዋል ይህ ለምን ተደረገ ? በማለት ጠይቀናቸዋል።
አቶ ጌታቸው ፤ " እኔ የጸጥታ ኃላፊ ሆኘ የምመራው አካባቢ ላይ የደረሰ ማንኛውም አይነት ጥቃት የለም። ኦፕሬሽን የተሰራበት አሽፋ ቀበሌ ነው። በስነ ስርዓት የጽንፈኛ ካምፕ ነው የወደመው " ብለዋል።
" ሐሙስ በነበረው ኦፕሬሽን ላይ በተመሳሳይ ከዛ የተረፈው የታጠቀ ኃይል እንጂ መንግስት የቆመው ለንጹሐን ህዝብ ነው " ሲሉ አክለዋል።
ታዲያ ሳይገደሉባቸው ማልቀስን ከየት አመጡት ? በማለት ለቀረበላቸው ጥያቄ " ንጹሐን ሰዎች አልተጎዱም " ብለው ፤ " የጸጥታ ኃይል ላይ ብረት ያነሳ፣ የተኮሰ ኃይል ሰላማዊ ኃይል ነው ብለን አናምንም " ሲሉ መልሰዋል።
እንደ ጸጥታ ዘርፍ ኃላፊነትዎ የሞቱ ንጹሐን እንዳሉ ያውቃሉ ? ወጣቶቹስ የት ገቡ ? ለሚለው ጥያቄ ፥ " የሞቱ ሰዎች ፅንፈኞች ናቸው በእኛ እውቅና። ነገም እንዲህ አይነት እርምጃ እንወስዳለን " ብለዋል።
አክለው፣ " ሐሙስ በነበረ ኦፕሬሽን ላይ 3 ሰዎች በውጊያ መካከል ተይዘዋል። ሰላማዊ ሰዎች ናቸው፤ አሉ በሕይወት። ሕጋዊ የማጣራት ሥራ ይሰራባቸዋል። 37 ሰዎች አይደሉም " ነው ያሉት።
" ከዚያ ውጪ አሽፋ ላይ ደግሞ የተያዘ ሰው የለም። በውጊያ መካከል እርምጃ የተወሰደበት ሰው ሊኖር ይችላል " ያሉት ኃላፊው፣ " ውጊያ መካከል ንጹሐን ላይ ጉዳት አይደርስም ማለት አይደለም " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
tg-me.com/tikvahethiopia/88311
Create:
Last Update:
Last Update:
#Amahra
በአማራ ክልል አዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ጓጉሳ እሽኩዳዶ ወረዳ፣ “ የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ንጹሐንን ገድለዋል ” ሲሉ ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪዎች ፤ በአካባቢው ከ16 በላይ ንጹሐን መገደላቸው እና ከ37 በላይ ወጣቶች ታፍነው መወሰዳቸውን አመልክተው " ይንን ያደረጉት የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ናቸው " ብለዋል።
ግድያው የተፈጸመው አሽፋ ማርያም፣ አሽፋ አዲስ ዓለም እና ወንጀላ በሚባሉት ቦታዎች ከሰኔ 2 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ እንደሆነ ጠቁመዋል።
አሽፋ ቀበሌ 8 ሰዎች መገደላቸውን ከ8ቱ 2ቱ ቄሶች እንደሆኑ አንዲት እመጫትም ከእነ ልጇ እንደተገደለች ቀሪዎቹ ደግሞ ከ15 ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች እንደሆኑ አስረድተዋል።
ነዋሪዎቹ ፥ በወረዳው ' ፋኖዎች ' እንደነበሩ ከዛ በፊት መከላከያ እንዳልገባ ፤ ያለፈው እሁድ ግን ሌሊት 9 ሰዓት አካባቢ ከገባ በኋላ እዛ የነበሩ ፋኖዎች ምንም ሳይታኮሱ ነው ቦታውን ለቀው እንደሄዱና ከዛ በኋላ ንጹሐን እንደተገደሉ ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም የነዋሪዎቹን ቃል ይዞ የዞኑን የጸጥታ ኃላፊ አቶ ጌታቸው ቢሻውን አነጋግሯል።
" ነዋሪዎች ከ16 በላይ ንጹሐን ተገድለዋል፣ ከ37 በላይ ወጣቶች ታፍነው ተወስደዋል " ብለዋል ይህ ለምን ተደረገ ? በማለት ጠይቀናቸዋል።
አቶ ጌታቸው ፤ " እኔ የጸጥታ ኃላፊ ሆኘ የምመራው አካባቢ ላይ የደረሰ ማንኛውም አይነት ጥቃት የለም። ኦፕሬሽን የተሰራበት አሽፋ ቀበሌ ነው። በስነ ስርዓት የጽንፈኛ ካምፕ ነው የወደመው " ብለዋል።
" ሐሙስ በነበረው ኦፕሬሽን ላይ በተመሳሳይ ከዛ የተረፈው የታጠቀ ኃይል እንጂ መንግስት የቆመው ለንጹሐን ህዝብ ነው " ሲሉ አክለዋል።
ታዲያ ሳይገደሉባቸው ማልቀስን ከየት አመጡት ? በማለት ለቀረበላቸው ጥያቄ " ንጹሐን ሰዎች አልተጎዱም " ብለው ፤ " የጸጥታ ኃይል ላይ ብረት ያነሳ፣ የተኮሰ ኃይል ሰላማዊ ኃይል ነው ብለን አናምንም " ሲሉ መልሰዋል።
እንደ ጸጥታ ዘርፍ ኃላፊነትዎ የሞቱ ንጹሐን እንዳሉ ያውቃሉ ? ወጣቶቹስ የት ገቡ ? ለሚለው ጥያቄ ፥ " የሞቱ ሰዎች ፅንፈኞች ናቸው በእኛ እውቅና። ነገም እንዲህ አይነት እርምጃ እንወስዳለን " ብለዋል።
አክለው፣ " ሐሙስ በነበረ ኦፕሬሽን ላይ 3 ሰዎች በውጊያ መካከል ተይዘዋል። ሰላማዊ ሰዎች ናቸው፤ አሉ በሕይወት። ሕጋዊ የማጣራት ሥራ ይሰራባቸዋል። 37 ሰዎች አይደሉም " ነው ያሉት።
" ከዚያ ውጪ አሽፋ ላይ ደግሞ የተያዘ ሰው የለም። በውጊያ መካከል እርምጃ የተወሰደበት ሰው ሊኖር ይችላል " ያሉት ኃላፊው፣ " ውጊያ መካከል ንጹሐን ላይ ጉዳት አይደርስም ማለት አይደለም " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
በአማራ ክልል አዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ጓጉሳ እሽኩዳዶ ወረዳ፣ “ የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ንጹሐንን ገድለዋል ” ሲሉ ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪዎች ፤ በአካባቢው ከ16 በላይ ንጹሐን መገደላቸው እና ከ37 በላይ ወጣቶች ታፍነው መወሰዳቸውን አመልክተው " ይንን ያደረጉት የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ናቸው " ብለዋል።
ግድያው የተፈጸመው አሽፋ ማርያም፣ አሽፋ አዲስ ዓለም እና ወንጀላ በሚባሉት ቦታዎች ከሰኔ 2 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ እንደሆነ ጠቁመዋል።
አሽፋ ቀበሌ 8 ሰዎች መገደላቸውን ከ8ቱ 2ቱ ቄሶች እንደሆኑ አንዲት እመጫትም ከእነ ልጇ እንደተገደለች ቀሪዎቹ ደግሞ ከ15 ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች እንደሆኑ አስረድተዋል።
ነዋሪዎቹ ፥ በወረዳው ' ፋኖዎች ' እንደነበሩ ከዛ በፊት መከላከያ እንዳልገባ ፤ ያለፈው እሁድ ግን ሌሊት 9 ሰዓት አካባቢ ከገባ በኋላ እዛ የነበሩ ፋኖዎች ምንም ሳይታኮሱ ነው ቦታውን ለቀው እንደሄዱና ከዛ በኋላ ንጹሐን እንደተገደሉ ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም የነዋሪዎቹን ቃል ይዞ የዞኑን የጸጥታ ኃላፊ አቶ ጌታቸው ቢሻውን አነጋግሯል።
" ነዋሪዎች ከ16 በላይ ንጹሐን ተገድለዋል፣ ከ37 በላይ ወጣቶች ታፍነው ተወስደዋል " ብለዋል ይህ ለምን ተደረገ ? በማለት ጠይቀናቸዋል።
አቶ ጌታቸው ፤ " እኔ የጸጥታ ኃላፊ ሆኘ የምመራው አካባቢ ላይ የደረሰ ማንኛውም አይነት ጥቃት የለም። ኦፕሬሽን የተሰራበት አሽፋ ቀበሌ ነው። በስነ ስርዓት የጽንፈኛ ካምፕ ነው የወደመው " ብለዋል።
" ሐሙስ በነበረው ኦፕሬሽን ላይ በተመሳሳይ ከዛ የተረፈው የታጠቀ ኃይል እንጂ መንግስት የቆመው ለንጹሐን ህዝብ ነው " ሲሉ አክለዋል።
ታዲያ ሳይገደሉባቸው ማልቀስን ከየት አመጡት ? በማለት ለቀረበላቸው ጥያቄ " ንጹሐን ሰዎች አልተጎዱም " ብለው ፤ " የጸጥታ ኃይል ላይ ብረት ያነሳ፣ የተኮሰ ኃይል ሰላማዊ ኃይል ነው ብለን አናምንም " ሲሉ መልሰዋል።
እንደ ጸጥታ ዘርፍ ኃላፊነትዎ የሞቱ ንጹሐን እንዳሉ ያውቃሉ ? ወጣቶቹስ የት ገቡ ? ለሚለው ጥያቄ ፥ " የሞቱ ሰዎች ፅንፈኞች ናቸው በእኛ እውቅና። ነገም እንዲህ አይነት እርምጃ እንወስዳለን " ብለዋል።
አክለው፣ " ሐሙስ በነበረ ኦፕሬሽን ላይ 3 ሰዎች በውጊያ መካከል ተይዘዋል። ሰላማዊ ሰዎች ናቸው፤ አሉ በሕይወት። ሕጋዊ የማጣራት ሥራ ይሰራባቸዋል። 37 ሰዎች አይደሉም " ነው ያሉት።
" ከዚያ ውጪ አሽፋ ላይ ደግሞ የተያዘ ሰው የለም። በውጊያ መካከል እርምጃ የተወሰደበት ሰው ሊኖር ይችላል " ያሉት ኃላፊው፣ " ውጊያ መካከል ንጹሐን ላይ ጉዳት አይደርስም ማለት አይደለም " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
BY TIKVAH-ETHIOPIA
Share with your friend now:
tg-me.com/tikvahethiopia/88311